If You a returning customer
Sign In
Password forgotten? Click here.
If You a new customer
By creating an account at Tsehai Publishers you will be able to shop faster, be up to date on an orders status, and keep track of the orders you have previously made.
Continue
Click to enlarge
አቶ አዱኛ አማኑ (ኀዳር 5 ቀን 1931 ዓ.ም. ሚያዝያ 16 ቀን 1999 ዓ.ም) በቀድሞ ሸዋ ክፍለ ሀገር ጅባትና ሜጫ በተባለው ስፍራ ተወለዱ።የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ት/ቤት በ1952 ዓ.ም አጠናቀቁ። በዚህምቆይታቸው ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እጅ በርካታ ሽልማቶችን ተሸልመዋል። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ በወቅቱ ወደ ዩኒቨርስቲ የሚያስገባ ውጤት ቢኖራቸውም ሐረር በሚገኘው የመንፈሳዊ ጉባዔ ት/ቤት ለአራት ዓመታት በመምህርነት አገለገሉ። በኋላም አዲስ አበባ በመመለስበቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ገብተው በ1961 ዓ.ም. በታሪክና ሳይኮሎጂ የትምህርት መስክ በባችለር ዲግሪ ተመረቁ። በዚህን ወቅት ለመመረቂያ ያቀረቡት ጥናት በወቅቱ ታላቅ አክብሮትን ያስገኘላቸው ሲሆን ከሃምሳ ዓመት ብኋላም በዚህ መልኩ በመጽሐፍ ለህትመት ለመብቃት ችሏል።
በህይወት ዘመናቸውም በተለያዩ የሙያ መስኮች ሥልጠናዎች የወሰዱና ሥልጠናም በማዘጋጀት የሠጡ ሲሆን በበርካታ ማህበራዊና ቤተሰባዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከፍተኛና ጉልህ ሚና ተጫውተዋል።አቶ አዱኛ ተማሪ ከነበሩበት ጊዜ ጀምሮ በኢትዩጵያ ሔራልድና በአያሌ ጋዜጦችናመጽሔቶች በብዕር ስም በመፃፍ ይታወቁም ነበር። በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ከዚህ በተለያዩ የሥራ መደቦች በኤክስፐርትነት፣ በተመራማሪነት፣ በመምህርነትና በከፍተኛ ኃላፊነት አገልግለዋል።
ካላቸው ከፍተኛ የማስተማር ፍላጐት የተነሳ ከመደበኛ ሥራቸው በተጓዳኝ ለ35 ዓመታት በአለማያ ኮሌጅ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ በአባዲና ሰንደፋ የፖሊስ ኮሌጅ፣ በባንክና ኢንሹራንስ ኢንስቲትዩትና በሐረር መምህራን ማሰልጠኛ በመምህርነትምአገልግለዋል። ጡረታ ከወጡ በኋላም ቢሆን በተለያዩ ጊዚያት ስልጠና በመስጠት ተሳትፈዋል።
አቶ አዱኛ አማኑ ለእውነትና ፍትህ የኖሩ፣ ሀገር ወዳድ፣ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን የሚከታተሉና ጠንቅቀው የሚያውቁ እንዲሁም ታሪክ አንባቢና ተመራማሪ ነበሩ።
View All Products
View All Authors
Sign up for our newsletter
Subscribe
Copyright © 2025 Tsehai Publishers All Rights Reserved.