The Ethiopian Orthodox Church Becomes Autocephalous (Coming soon) [978-1-59-907253-1]

$14.95



Author : Adugna Amanu



ISBN Code : 978-1-59-907253-1
Language : Amharic
Pages number : 72
Format : Paperback

ታሪክ እንደሚያስረዳው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን አጥቢያ ሆና ለ1,600 ዓመታት በላይ ኖራለች። ቤተክርስቲያኗ በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአሌክሳንድርያው ፓትርያርክ በተሾሙት በአቡነ ሰላማ መሪነት ብሔራዊ ቁመና ኖሯት እንደተመሰረተችም የኢትዮጵያና የግብፅ መዛግብት ያመለክታሉ። በሰኔ 21 ቀን 1951 ዓ.ም አቡነ ባስልዮስ ብጹዕ ወቅዱስ ተብለው የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ሆነው ሲሾሙ ከሃያ አምስት ዓመታት በላይ የዘለቀው ትግል ፍጻሜ አገኘ።

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በአማኝ ብዛት ተጣምረው ከምትበልጣቸው ከግብጽ: ኮፕቲክ)፣ ከሶሪያ፣ አርመን እና ማላንካር ሲሪያክ (ህንድ) ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያናት ጋር በመሆን የ5ኛውን ክፍለ ዘመን የአሌክሳንድርያንና አንፆኪያን ሊቃነ ጳጳሳት ምሳሌ በመከተል እ.ኤ.አ ግብፆች በ451 ዓ.ም “ተላልፏል” የሚሉትን፤ ግን ደግሞ ማስረጃ ያልተገኘለትን የኬልቄዶን ጉባኤ ውሳኔ አልተቀበለችውም። ሆኖም እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በአሌክሳንድርያው ሊቀጳጳስ ሥር ነበረች።

የኢትዮጵያ ታሪክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ላይ ወደዘመናዊው ምዕራፍ ሲሸጋገር ለቤተክርስቲያኗ ይሰጥ የነበረው ትኩረት ተቋረጠ፤ ቤተክርስቲያኗ እና መሪዎቿ ከነበራቸው ማዕከላዊ ሚና ከነአካቴው ተነጠሉ፤ የዕውቀት ጣሪያ መለኪያ የነበሩት ሃይማኖታዊ ክርክሮችም ከምህዳር ድንገት ጠፉ። የተወሳሰበው የዘመናዊ ብሔራዊ መንግሥት እሳቤም ለዘመናት የዳበረውን የህብረተሰቡን መንፈሳዊ ሕይወትና እሴት ወደጎን ገፋው። በሂደቱም በሚሊዮኖች ሕይወት ውስጥ ጉልህ ድርሻ የነበራትና ያላት ብሎም ከተከታዮቿ ማንነትና የዘመናዊነት አመለካከት ጋር በእጅጉ የተቆራኘችው ቤተክርስቲያን በዘመናዊው የኢትዮጵያ ጥናት የሚገባትን ድርሻ ሳታገኝ ቀረች።

መቅድም

የደራሲው ማስታወሻ

ምዕራፍ 1፡ መግቢያ

ምዕራፍ 2፡ ማዕረገ-ጵጵስናን በከፊል ኢትዮጵያዊ የማድረግ ሂደት (1929-35)

ምዕራፍ 3፡ የጣልያን ወረራ (1936-41)

ምዕራፍ 4፡ ጥግ ድረስ የሄደው ማዕረገ-ከፍታ

ምዕራፍ 5፡ ራስን በራስ የማስተዳደር ነፃነትን ማግኘት በቤተ-ክርስቲያን ውስጥ ለውጥ አምጥቷልን?

ዋቢ መጻሕፍት

አባሪ

Close window